ዓለምና ዘመን ፊታቸውን ያዙሩባት ሀገር!

በፍኖተ ዴሞክራሲ የኢትዮጵያ አንድነት ድምጽ:  በዘረኝነት ላይ የተመሰረተ አምባገነን አገዛዝ በኢትዮጵያ ከተንሰራፋ ፤ይኸው ሠላሣ ዓመታት እያስቆጠረ ነው።  በዘመን ስሌት ሲቆጠር ቀላል ጊዜ አይደለም።  የአንድ መሥዋዕታዊ ትውልድ ዘመን አሳልፎ ሌላ ትውልድ እየተካ ይገኛል።  ይህ ዘመን፤  በሀገራችን ታሪክ ዜና መዋዕል፤ የመከራ፤ የውርደት፤ የሀፍረት፤ የጥፋት፤ የጥቃት፤ ሀገር የመቆራረስና ሕዝብ የመከፋፈል ሀቅን መዝግቧል። በዚህ ዕኩይ ዘመን፤ የሀገሪቱ ዳር-ድንበር ተደፍሯል።  ሀገራዊ ወሰኗ የት ላይ እንደሚቆም እንኳን ገና አልታወቀም!  ሙሉውን ያንብቡ…